ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፣ ክርስቶስን የሚያውቅና የእርሱ ተከታይ የሆነ እማኝ ዋነኛው የባህሪው መገለጫ ፍቅር ሊሆን ይገባል፣ ጌታ እየሱስ እንኳን አንድ ሕግ አዋቂ ሊፈትነው ከሕግ የትኛይቱ ትእዛዝ ታላቅ እንደሆነች ሲጠይቀው የመለሰው መልስ፣ ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍሥህም በፍጹም አሳብህም ውደድ ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች፥ እርስዋም ባልንጀራህን እንደ ነፍሥህ ውደድ የምትለው ናት ብሎ ነው፣ እንግዲህ በዚህ ፍቅር ለማደግ የመጀመሪያው ይቅር ማለት ሲሆን በመቀጠል ፍቅርን መከታተልና ከቅዱሳን ጋር ጤነኛ ህብረትን በመፍጠር ልንገለጽ ይገባናል፣ ክርስቶስ በምን ያህል ፍቅር እንደወደደን ሲገባን ሌሎችን ለመውደድ አንቸገርም፣