እግዚአብሔር ስለ ስሙ የሚሰራ አምላክ ነው። ጌታ ስለ ስሙ ሲሰራ ጸሎቴ ነው ልመናዬ ነው ብለን ልንመካ አንችልም፣ ካልንም ትዕቢት ነው። እግዚአብሔር ማንኛውንም ነገር በህይወታችን የሚሰራው ስለተቀደሰ እና ስለ ታላቅ ስሙ ነው። በእኛ ላይ ስለተጠራው ስሙ ሲል ይባርከናል የሚያስፈልገንን ይሰጠናል።ስለዚህ ልመናችንና ጸሎታችን ምስክርነታችን እንጂ ትምክህታችን ሊሆን አይገባም።ስሙ ከስሞች ሁሉ በላይ ነው። አጋንንትን ያንቅጠቅጣል ፣ ያስወጣል፣በሽታንም ይፈውሳል።