የምንኖርበት ይህ አለም በብዙ የሚያደክም ደግሞም የሚያታክት እንደሆነ ግልፅ ነው:: የእግዚአብሔርን ፊት በመፈለግና እርሱን በመጠበቅ ግን አንዳንታክት እንዳንደክምም ቅዱስ ቃሉ ይመክረናል:: በእምነት እግዚአብሔርን መጠበቅ በውስጡ ሀይል አለው ተስፋ አለው ክብር አለው:: እግዚአብሔር በቃሉ የታመነ ነውና::